የሀገር ውስጥ ዜና

የጥቁር ገበያ ምንዛሬ ኢትዮጵያን የማዳከም ዘመቻ አካል መሆኑን ተገንዝበን ህጋዊ አማራጭ ልንጠቀም ይገባል – አቶ አቤ ሳኖ

By Feven Bishaw

December 05, 2021

አዲስ አበባ፣ህዳር 26፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥቁር ገበያ ምንዛሬ ኢትዮጵያን የማዳከም ዘመቻ አካል በመሆኑ “ህጋዊ የምንዛሬ አማራጮችን ብቻ መጠቀም ይገባል” ሲሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገለጹ፡፡

አቶ አቤ ሳኖ፤ በህገ-ወጥ መንገድ የሚመነዘር የውጭ አገር ገንዘብ በአመዛኙ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ለሚሰሩ ኃይሎች እንደሚውል ነው የተናገሩት፡፡