የሀገር ውስጥ ዜና

የብሬክስሩ ኒውስ ጋዜጠኞች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የከተማዋን ሰላማዊነት ለዓለም በማሳየት ላይ ናቸው

By Mekoya Hailemariam

December 05, 2021

አዲስ አበባ፣ ህዳር 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)  የምዕራባውያኑ መገናኛ ብዙሃን ከዓለም የሚደብቁትን እውነታ በመግለጥ የሚታወቁት የብሬክስሩ ኒውስ ጋዜጠኞች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የከተማዋን ሰላማዊነት ለዓለም በማሳየት ላይ ናቸው።

ጋዜጠኛ ኢዩጂን ፒሩየር እና ራኒያ ካሌክ አዲስ አበባ መግባታቸውንና በሚቀጥሉት ቀናት ስለ አፍሪካ ቀንድ እውነተኛ ዘገባዎችን ለዓለም እንደሚያደርሱ ተናግረዋል።

አንድነት ፓርክንና የወዳጅነት አደባባይን ጨምሮ ከተማዋን ተዘዋውሮ የተመለከተው ጋዜጠኛ ኢዩጂን “ስለ አዲሰ አበባ ሊዘገብ የሚችለው ሰላማዊ እና በፈጣን እንቅስቃሴ ውስጥ መሆኗን ብቻ ነው” ብሏል።

አያይዞም የወዳጅነት አደባባይ ሰርገኞችን እና ሌሎች ጎብኚዎችን እያስተናገደ ስራ ብዙ መሆኑን በምስል አስደግፎ አቅርቧል።

One thing I can report: Addis is calm and relaxed. Daily life is proceeding apace. The fear mongering about the situation here is totally unfounded pic.twitter.com/bp6CSkBcBn

— Eugene Puryear (@EugenePuryear) December 4, 2021

ራኒያ ካሌክ በበኩሏ “አዲስ አበባን ተዘዋውረን አይተናታል የውጭ መገናኛ ብዙሃኑ እንደሚያናፍሱት በህወሃት እጅ ለመውደቅ የተዘጋጀች አሊያም የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንደሚያስጠነቅቀው የተረበሸች ወይም የምታስፈራ ከተማ አይደለችም ብላለች” የመዲናይቱን ሰላማዊነት ስትገልፅ።

ቢቲ ኒውስ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ ላይ እውነትን ለዓለም የገለጡ በርካታ ጥንቅሮችን በማዘጋጀት አሰራጭቷል።

የምእራቡን ዓለም ሴራ የሚያጋልጡ ዘገባዎችን በመስራት ነፃ ድምፅ መሆኑ የሚነገርለት ይህ ሚዲያ ቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት የሀገሪቱን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማሳየት የራሱ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ይጠበቃል።