የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ 17ኛውን የኢንተርኔት አስተዳደር ፎረም ታስተናግዳለች

By Feven Bishaw

December 07, 2021

አዲስ አበባ፣ ህዳር 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በ2015 የሚካሄደውን 17ኛውን የኢንተርኔት አስተዳደር ፎረም እንደምታስተናግድ ተገለፀ፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁርያ አሊ ከተባበሩት መንግስታት የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሉ ዤንሜን ጋር በፎረሙ ዝግጅት ዙሪያ በፖላንድ ተወያይተዋል።