የሀገር ውስጥ ዜና

ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እየተጠገነ ነው

By Feven Bishaw

December 07, 2021

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 28 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከገረገራ እስከ ጋሸና ያለውን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የመጠገን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታወቀ፡፡

ከህዳር 23 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደ የፍተሻ ሥራ 34 በሚሆኑ ታወሮች መካከል በሚገኙ ቦታዎች ላይ 50 የመስመሮች መበጣጠስ፣ 7 የድምፅና ዳታ ማስተላለፊያ የኦፕቲካል ፋይበር መቆረጥ እና 13 ቦታዎች ላይ መስመር ሳይበጠስ ጉዳት መድረሱን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡