የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል በህወሓት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ሥራ ለማስጀመር ከ11 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ

By Feven Bishaw

December 10, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በአሸባሪው በህወሓት የወደሙ ከ4 ሺህ የሚበልጡ የትምህርት ተቋማትን መልሶ ሥራ ለማስጀመር ከ11 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡

አሸባሪው ህወሓት በክልሉ ያወደማቸው የትምህርት ተቋማትን መልሶ ለመገንባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።