የሀገር ውስጥ ዜና

በቀድሞው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ሃላፊዎች ላይ ፍርድ እና ብይን ተሰጠ

By Feven Bishaw

December 10, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 1 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀድሞው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ጌታቸው አሰፋ ፣ ያሬድ ዘሪሁን እና ሌሎች 24 ተከሳሾች ላይ ፍርድ እና ብይን ተሰጠ ።

ተከሳሾቹ ከ1984 ዓ.ም እስከ 2010 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ውስጥ በቀድሞው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት መስሪያቤት በተለያዩ የስራ ሃላፊነቶች ተመድበው ሲሰሩ በህግ አግባብ የተሰጣቸውን ስልጣን መሰረት በማድረግ በአገሪቱ የተለያዩ ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ ባሉ ክፍለ ከተሞች፣ በአማራ ክልል ባህርዳርና ጎንደር፣ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ፣ ጅማ፣ ሻሸመኔና ቢሾፍቱ፣ በደቡብ ክልል ሀዋሳ ከተማ ሰዎች የሚታሰሩበትን ሁኔታ በማመቻቸትና ድብቅ እስር ቤቶችና መመርመሪያ ክፍሎች እንዲዘጋጁ ማድረጋቸው ተጠቅሷል።