አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳንድ ድርጅት /ኔቶ/ መስፋፋት ጋር በተያያዘ ከምእራባውያኑ ጋር አስቸኳይ ውይይት ማድረግ እንደምትፈልግ አስታወቀች።
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸው ከዩክሬን ጋር በምትዋሰንበት ድንበር ላይ የተፈጠረውን ውጥረት አስመልክቶ የሞስኮን የደህንነት ችግር አደጋ ላይ እንዳይጥል የሚያስችል ዋስትና ለማግኘት ከአሜሪካ እና ከኔቶ ጋር በአስቸኳይ መነጋገር እፈልጋለሁ ብለዋል ፡፡