ቢዝነስ

በአምስት ወራት ውስጥ 147 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰበሰበ

By Feven Bishaw

December 15, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአምስት ወራት ውስጥ 147 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፥ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ የኮሮና ወረርሽኝን፣ አገራዊ የፀጥታና መሰል ተግዳሮቶችን በመቋቋም 147 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።