ፋና ስብስብ

ወድቆ ያገኙትን 3 ሺህ 900 ዶላር ያስረከቡት የፖሊስ አባላት

By Feven Bishaw

December 16, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አራት የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ወድቆ ያገኙትን 3 ሺህ 900 የአሜሪካ ዶላር ማስረከባቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ምክትል ኢንስፔክተር ዘነበ እሸቱ ፣ምክትል ኢንስፔክተር ዳግም ግርማ እና ዋና ሳጅን አለምነሽ ግርማ የተባሉ የአቃቂ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አባላት በጥበቃ ስራ ላይ እያሉ ቆሻሻ በተደረገበት ፌስታል ውስጥ የተጠቀለለ 1 ሺህ 900 ዶላር አግኝተው ለአቃቂ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አስረክበዋል፡፡