አዲስ አበባ ፣ ታህሳሰ 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ÷ ወቅቱ የበዓላት መሆኑን ጠቅሰው በኢትዮጵያ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት በዓሉን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማክበር እየሄዱ መሆኑን አስታውቀዋል።
አያይዘውም “እኛም በታላቁ የወደሀገር ቤት ኑ ዘመቻ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን እንቀበላለን” ብለዋል።
አካባቢዎን ይጠብቁ! ወደ ግንባር ይዝመቱ! መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!