የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ በልጆቿ የመተባበርና የመተሳሰብ ባህል ሊገጥማት የሚችለውን የምጣኔ ኃብት ማሽቆልቆል መቋቋም ትችላለች – የምጣኔ ኃብት ምሁራን

By Feven Bishaw

December 17, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 8 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በልጆቿ የመተባበርና የመተሳሰብ ባህል ሊገጥማት የሚችለውን የምጣኔ ኃብት ማሽቆልቆል መቋቋም እንደምትችል በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ኃብት ምሁራን ገለጹ።

ምሁራኑ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከጦርነቱ በኋላ ሊገጥማት የሚችለውን የኢኮኖሚ ድቀት ለማካካስ ከወትሮው በተለየ ግብርናን በማጠናከር ምርታማነትን ማሳደግ ይገባታል።