የሀገር ውስጥ ዜና

ከ1 ሺህ 400 በላይ የክላሽን-ኮቭ ጠብመንጃ ጥይት ተያዘ

By Feven Bishaw

December 17, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 8 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ በተሽከርካሪ ተጭኖ ሲጓጓዝ የነበረ ከ1 ሺህ 400 በላይ የክላሽን-ኮቭ ጠብመንጃ ጥይት በህብረተሰቡ ጥቆማ መያዙን ገለፀ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ ለፖሊስ አባላቱ 800 ሺህ ብር መደለያ እንስጣችሁ ቢሉም የፖሊስ አባላቱ መደለያውን ወደ ጎን በመተው ተጠርጣሪዎቹን ለህግ ማቅረባቸውንም አስታውቋል፡፡