የሀገር ውስጥ ዜና

ለዱባይ ኤክስፖ 2020 ዝግጅት የግንባታ ሂደት 10 ሺህ ኢትዮጵያውያን እንዲሳተፉ ከስምምነት ተደረሰ

By Tibebu Kebede

February 15, 2020

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 7፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የዱባይ 2020 ኤክስፖ በሚካሄድበት ስፍራ እየተደረገ ያለውን ዝግጅት ጎበኙ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው በዛሬው ዕለት ዱባይ 2020 ለተሰኘው ኤክስፖ እየተከናወኑ ያሉ ዝግጅቶችን ጎብኝተዋል።