የሀገር ውስጥ ዜና

ከለቡ-ጀሞ የብስክሌት ትራንስፖርት አገልግሎት ስራ ጀመረ

By Tibebu Kebede

February 16, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ከለቡ ጀሞ የተሰራውን የሞተር አልባ ትራንፖርት አገልግሎት መስጫ መንገድ ስራ መጀመሩን የከተማዋ የትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።

የብስክሌት ትራንስፖርት አገልግሎት የጀመረው ነዋሪው ብስክሌትን እንደ አንድ የትራንስፖርት አማራጭ እንዲጠቀም ታስቦ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ስጦታው አካለ ተናግረዋል።