የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል ከህወሃት ወረራ ነጻ በወጡ አካባቢዎች ለሚገኙ ወገኖች በየወሩ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል እህል ያስፈልጋል

By Feven Bishaw

December 25, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በአማራ ክልል አሸባሪው ህወሓት በወረራ በቆየባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በየወሩ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል የምግብ እህል እንደሚያስፈልግ የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽነሩ አቶ ዘላለም ልጃለም ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ አሸባሪው ህወሓት በክልሉ በወረራ ይዟቸው በቆዩ ሰባት ዞኖች ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት አድርሷል።