አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በአማራ ክልል አሸባሪው ህወሓት በወረራ በቆየባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በየወሩ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል የምግብ እህል እንደሚያስፈልግ የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ።
ኮሚሽነሩ አቶ ዘላለም ልጃለም ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ አሸባሪው ህወሓት በክልሉ በወረራ ይዟቸው በቆዩ ሰባት ዞኖች ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት አድርሷል።