የሀገር ውስጥ ዜና

የደላንታ ወረዳ ወገልጤና ከተማ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በአሸባሪው ቡድን እስከ 1 ቢሊየን ብር የሚገመት ሀብት እንደወደመበት ገለጸ

By Meseret Awoke

December 26, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደላንታ ወረዳ ወገልጤና ከተማ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ በአሸባሪው እና ዘራፊው ቡድን ከ900 ሚሊየን እስከ 1 ቢሊየን ብር የሚገመት ሀብት እንደወደመበት ገለጸ።

የአሸባሪው ህወሓት ሃይሎች በኮሌጁ የነበሩ ሃብቶችን እና የመማሪያ ቁሳቁሶችን መዝረፋቸውን እና መዝረፍ ያልቻሉትን ባለበት ማውደማቸውን የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ዓለሙ ዘውዱ ተናግረዋል።

በዘረፋ እና በውድመቱ ምክንያት ኮሌጁ አሁን ምንም አይነት የትምህርት አገልግሎት መስጠት እንደማይችል ተነግሯል።

በለይኩን ዓለም

አካባቢዎን ይጠብቁ! ወደ ግንባር ይዝመቱ! መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!