የሀገር ውስጥ ዜና

በ”አንድ ብር ለሠብዓዊነት” 120 ሚሊየን ብር ለማሰባሰብ ያለመ መርሃ ግብር ተጀመረ

By Feven Bishaw

December 27, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 18 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ በመዘዋወር ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች የሚውል 120 ሚሊየን ብር ማሰባሰብን ዓላማ ያደረገ “አንድ ብር ለሠብዓዊነት” የተሰኘ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ተጀምሯል።

መርሃግብሩ ስለ ፍቅር ኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ድርጅት ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እና ከአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ ጋር በመተባበር የሚያካሂደው ነው ተብሏል።