አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 18 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ በመዘዋወር ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች የሚውል 120 ሚሊየን ብር ማሰባሰብን ዓላማ ያደረገ “አንድ ብር ለሠብዓዊነት” የተሰኘ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ተጀምሯል።
መርሃግብሩ ስለ ፍቅር ኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ድርጅት ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እና ከአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ ጋር በመተባበር የሚያካሂደው ነው ተብሏል።