የሀገር ውስጥ ዜና

በድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፊያ የጦር መሳሪያ ፍንዳታ ተከሰተ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሐሰት ነው – የፌደራል ፖሊስ

By ዮሐንስ ደርበው

December 27, 2021

ይህንን የኤሌክትሪክ አደጋ አንዳንድ ግለሰቦች በአሸባሪው ህወሓትና ሸኔ ቡድን የፀጥታ ችግር እንደተከሰተ እና የተኩስ ልውውጥም እንደተፈጠረ አስመስለው ውዥንብር በመፍጠር ሐሰተኛ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያ ቢያሰራጩም ምንም አይነት የፀጥታ ችግር እንዳልተከሰተና አውሮፕላን ማረፊያው የተለመደ በረራውን እያካሄደ መሆኑንም ነው የገለጹት።

የአሸባሪ ህወሓት ጁንታና የሸኔ ቡድን በነገው ዕለት በቁልቢ የሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል ለማደናቀፍና በዓሉ በሰላማዊ መንገድ ተከብሮ እንዳይጠናቀቅ ሐሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆናቸውን ፖሊስ ደርሶበታል ብለዋል፡፡

በመሆኑም ህብረተሰቡ ይህንን በመገንዘብ ምንጩ ባልታወቀ ሐሰተኛ መረጃ ሳይደናገር እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በዓሉን በሰላማዊ መንገድ እንዲያከብር ጥሪ አስተላልፈዋል።