ኮሮናቫይረስ

የሰሞኑ ጉንፋን ጉዳይ!

By Mekoya Hailemariam

December 28, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)  ሰሞኑን ወረርሽ በሚመስል መልኩ በርካቶች በዚህ ህመም ተይዘዋል። የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልም ለዚህ የሰሞኑ ጉንፋን ጠቃሚ መረጃን በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይዞ ወጥቷል።

የሰሞኑ ጉንፋን ለየት የሚያረገው ግን ከፍተኛ ትኩሳት እና ጠንከር ያለ ሳል አለው በተጨማሪም እነዝህ ምልክቶች ይታዩበታል፡፡

ምክንያቱ ምን ሊሆን ይችላል?

ጉንፋን ዋና መንስኤዎቹ በትንፋሽ በሳል እና በማስነጠስ የሚተላለፉ ቫይረሶች ናቸው ::ለምሳሌ÷ ኮሮና ቫይረስ ፣ራይኖ ቫይረስ፣ ኢንፍሉዌንዛ አዴኖ ቫይረስ እና የመሳሰሉት ጉንፋንን ሊያመጡ ይችላሉ፡፡ስለዚህ የሰሞኑ ጉንፋን ኮሮና ይሁን አይሁን የሚታወቀው በምርመራ ብቻ ነው:: ስለዚህ ምን እናድርግ?

ለልጆች እና ህፃናት የቤት ዉስጥ ሕክምናው ምንድነው?

ለታዳጊ ህፃናት እና ለአዋቂዎችስ የቤት ዉስጥ ሕክምናው ምንድነው?

ከላይ ከተዘረዘሩት በተጨማሪ ራስን በአንድ ክፍል ማግለል

ትኩስ ፈሳሽ ነገሮችን ደጋግሞ መውሰድ

ነጭ ሽንኩርት ማር እና ዝንጅብል መጠቀም

በቂ እረፍት ማድረግ

የትኩሳት እና ራስ ምታት ማስታገሻ መውሰድ

እነዚህን መፍትሄዎ እያረጋችሁ ምንም ለውጥ ከሌለው እና ሳሉ የመባስ ትኩሳቱ የመጨመር ባህሪ ካለው ወይም ትንፋሽ የማጠር ምልክት በህፃንም ሆነ በአዋቂ ላይ ካለ በአፋጣኝ ሆስፒታል መሄድ ያስፈልጋል፡፡

 

በዶ/ር ፋሲል መንበረ  በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር እና የሕጻናት ስፔሻሊስት ሐኪም