የሀገር ውስጥ ዜና

ክልሎች የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚያደርጉት ድጋፍ ኢትዮጵያዊነት ያመጣው ስሜት ነው – ዶክተር ከይረዲን

By Feven Bishaw

December 30, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ክልሎችና ተቋማት የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚያደርጉት ድጋፍ ቁስ ለመስጠት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊነት ስሜት ያመጣው አንድነት ነው ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንትሮፖሎጂስትና የብዝሀነት ተመራማሪ ዶክተር ከይረዲን ተዘራ ገለጹ፡፡

አሸባሪው ህወሓት ከቁስ በዘለለ በኢትዮጵያ የአብሮነት እሴት ላይ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊና በስነ-ልቦናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ጉዳት ማድረሱን እና አደጋው ጥልቀት ያለው መሆኑን ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡