የሀገር ውስጥ ዜና

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና የብሉናይል ግዛት በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ

By Feven Bishaw

December 30, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና የብሉናይል ግዛት ከዚህ ቀደም የነበራቸውን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

በአሶሳ ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው በኢትዮጵያ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና በሱዳን የብሉናይል ግዛት የጋራ የድንበር ልማት ትብብር ውይይት ዛሬ ተጠናቋል፡፡