Fana: At a Speed of Life!

ኒጀር የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል በመሆን ባገለገለችበት ወቅት አህጉራችንን አኩርታለች- ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ

 

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኒጀር የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል በመሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ባገለገለችበት ወቅት ላሳየችው መርህን፣ ጨዋነትንና የአፍሪካ አንድነትን ማዕከል ያደረገ አቋም አገራችንንና አህጉራችንን ያኮራች በመሆኗ ለኒጀር መንግሥት እና ፕሬዚዳንት ምስጋና እና አድናቆት ይገባታል ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ተናገሩ፡፡

ፕሬዚዳንቷ ይህን ያሉት የቆይታ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የኒጀርን አምባሳደር ባሰናበቱበት ወቅት ነው፡፡

ከፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ እንደሚያመላክተው÷ አምባሳደሩ ባለፉት ስድስት ዓመታት የሁለቱን አገራት ግንኙነት ለማጠናከር ላደረጉት ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ከሰባት ወራት በፊት በኒጀር የሥራ ጉብኝት አድርገው እንደነበርና በ 90 ዎቹ በኒጀር በተካሄዱ ሁለት ምርጫዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የታዛቢዎች ቡድንን መምራታቸው ይታወሳል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.