የሀገር ውስጥ ዜና

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እጩ ኮሚሽነሮች አቀራረብ ስርዓት ተዘረጋ

By Melaku Gedif

January 03, 2022

 

አማካሪ ቡድኑ በምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ የሚመራ ሲሆን÷ የፌዴሬሽን ምክርቤት አፈ ጉባኤ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት እንዲሁም የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና  የሲቪክ ማህበራት ጥምረት ተወካዮች በአባልነት ተካተውበታል፡፡

ቡድኑ የተለያዩ ተግባራት እና ኃላፊነቶች የተሰጡት መሆኑን የጠቀሱት አፈ ጉባኤው÷ ከቀረቡ እጩዎች ውስጥ በአዋጁ ላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች በከፍተኛ ደረጃ የሚያሟሉትን እጩዎች በመለየት ረገድ አፈ ጉባኤውን ማማከር ዋነኛው ስለመሆኑ ዛሬ በተደረገው ውይይት ላይ ጠቁመዋል፡፡

የጥቆማ መስጫ መርሃ ግብርና ጥቆማ የሚሰጥበት ፎርማት ገና ይፋ ሳይደረግ ጥቆማዎች እየቀረቡ ስለመሆኑ አፈ ጉባኤው ገልጸው÷ እነዚህ ጥቆማዎችም ተቀባይነት እንደማይኖራቸው ማስገንዘባቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እጩ ኮሚሽነሮች ማቅረቢያ ጊዜ፣  ፎርማትና አጠቃላይ የእጩዎች አቀራረብ ስርዓትን በተመለከተ አፈጉባኤው ዛሬ ከሰዓት በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡