አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢንዱስትሪ መንደርነታቸው በሚታወቁት ዱከም እና ገላን ከተሞች ዲያስፖራው በኢንቨስትመንት ዘርፍ እንዲሰማራ የከተማዎቹ አስተዳደሮች ጥሪ አቀረቡ።
በከተሞቹ ከዚህ ቀደም በርካታ የሀገር ውስጥ እና የወጭ ባለሀብቶች በተለየያዩ የኢቨስትመንት መስከሎች ተሰማርተዋል ያሉት የየከተሞቹ አስተዳደር የስራ ሀላፊዎች ፣ አሁን ላይ መንግስት ያቀረበውን ጥሪ ተቀብለው ወደ ሀገር ቤት የገቡ የዲያስፖራው ማህበረሰብ አባላት ወደ ከተሞቹ በመምጣት እንዲያለሙ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።