አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 27፣ 2014 ( ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር ስኬታማ እንዲሆን መንግስት፣ ልሂቃን፣የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁሉም ተሳታፊዎች የመጨረሻውን ስምምነት የማክበር ሃላፊነት አለባቸው ሲሉ የፖለቲካል ሳይንስ ምሁራን ገለጹ፡፡
በኮተቤ ትምህርት ዩንቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር የሆኑት ዶክተር አየነው ብርሀኑ÷ በሚደረገው ሀገራዊ ምክክር ሁሉም ተሳታፊዎች በሀሳብ የበላይነት ለማመን እንዲሁም የሚደረስበትን ውጤት ለመቀበል ቁርጠኛ መሆን ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡