አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 28፣ 2014 ( ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያውያን እሴቶች የሆኑትን ፍቅርንና አንድነትን በማጠናከር የልደት በዓሉን ማክበር እንደሚገባ የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የገና በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት ገለጸ፡፡
የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በድል ማግስት ለሚከበረው የብርሃነ ልደቱ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ሲል መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡