ስፓርት

በጣሊያን በተካሄደ አገር አቋራጭ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

By Meseret Awoke

January 07, 2022

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አትሌቲክስ ቱር አካል በሆነውና በጣሊያን በተደረገው አገር አቋራጭ የአትሌቲክስ ውድድር አትሌት ዳዊት ስዩምና ይሁኔ አዲሱ በሁለቱም ፆታዎች አንደኛ በመውጣት አሸንፈዋል፡፡

በወንዶች 10 ኪሎ ሜትር ይሁኔ አዲሱ በ28 ደቂቃ ከ39 ሰከንድ 1ኛ ደረጃን ይዟል፡፡

በሴቶች 6 ኪሎ ሜትር ዳዊት ስዩም በ18 ደቂቃ ከ48 ሰከንድ 1ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ፋንታዬ በላይነህ እና መዲና ኢሳ 4ኛ እና 5ኛ ደረጃ ይዘው ውድድሩን ማጠናቀቃቸውን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!