የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያየ

By Feven Bishaw

January 08, 2022

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በድህረ ጦርነት ዝንፈቶችና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያየ፡፡

የውይይቱን መነሻ ሀሳብ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፉክክራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በጦርነቱ ወቅት ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ በማሰባሰብ እና የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን የሚያወግዙ ፣ የህዝብ ንቅናቄዎችን በጋራ በመፍጠር በአንድነት በመቆም አገራቸውን መታደጋቸውን አስረድተዋል።