ጤና

የኮሮና ቫይረስ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ተባለ

By Tibebu Kebede

February 18, 2020

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የኮሮና ቫይረስ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ባለድርሻ አካላትና የክልል መስተዳድሮች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢንስቲትዩቱን የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡