የሀገር ውስጥ ዜና

በጉራፋርዳ ወረዳ ከተከሰተው ሁከት ጋር በተያያዘ የወረዳው አስተዳዳሪን ጨምሮ የተለያዩ ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

By Tibebu Kebede

February 18, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል ጉራፋርዳ ወረዳ በትናንትናው ዕለት ከተከሰተው ሁከት እና ብጥብጥ ጋር በተያያዘ የወረዳው አስተዳዳሪን ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በአሁኑ ወቅት የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ ተከትሎ በክልሉ ህግን የማስከበር እና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ሥራ በልዩ ሁኔታ መጀመሩን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።