አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠንካራና ቅቡልነት ያለው ሀገረ መንግስትን በመገንባት ሂደት ሚናው ከፍተኛ በሆነውና በቅርቡ እንደሚካሄድ በሚጠበቀው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ሁሉም ዜጋ ሃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት አለበት ሲሉ ምሁራን ተናገሩ ፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ የታሪክ እና የህግ ምሁራን የዕጩ ኮሚሽነሮችን ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ ያሉ አጋጣሚዎችን በአግባቡ በመጠቀም በቀጣይ ሂደቶች ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡