የሀገር ውስጥ ዜና

የአሸባሪው ሸኔ የጥፋት ድርጊትን ለመመከት የበኩላችንን እየተወጣን ነው – ወጣቶች

By Feven Bishaw

January 22, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው ሸኔ በሰውና ንብረት ላይ የሚፈጽመውን የጥፋት ድርጊት ለመመከት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን በምዕራብ ወለጋ ዞን አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች ገለጹ።

ወጣቶቹ የአሸባሪ ቡድኑን አስነዋሪ ተግባር ለማስቆም ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ ነው ያመለከቱት።