የሀገር ውስጥ ዜና

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጤና ሳይንስ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

By Feven Bishaw

January 22, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጤና ሳይንስ ያሰለጠናቸውን ለ15ኛ ዙር ፤ በህክምና ስፔሻሊቲ ያሰለጠናቸውን ደግሞ ለ6ኛ ዙር አስመረቀ።

ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ዕለት 246 ቅድመ ምረቃ ፣ 74 በ2ኛ ዲግሪና እና 40 የህክምና ስፔሻሊስቶችን ጨምሮ 360 ተማሪዎችን ማስመረቁን የኮሌጁ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንተነህ ጋዲሳ ተናግረዋል፡፡