የሀገር ውስጥ ዜና

ሁሉም የፌዴራል ጠበቆች በነቂስ ወጥተው በጠበቆች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ

By Feven Bishaw

January 22, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁሉም የፌዴራል ጠበቆች በነቂስ ወጥተው ጥር 15 በሚካሄደው የጠበቆች ጠቅላላ ጉባኤው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የፍትሕ ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ጠቅላላ ጉባኤን አስመልክቶ የኢፌዴሪ የፍትሕ ሚኒስቴር ማምሻውን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ፥ ለአገራችን የፍትህ ስርዓትና ለሙያው ዕድገት ብሎም ለሕረተሰቡ የተሻለ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የጠበቆች ጠቅላላ ጉባኤ ወሳኝ ሚና ያለው መሆኑን ከግምት በማስገባት ሁሉም የፌዴራል ጠበቆች በነቂስ ወጥተው በጠቅላላ ጉባኤው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አስተላልፏል፡፡