ቢዝነስ

ኢትዮጵያ በግማሽ ዓመቱ 39 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ብድርና እርዳታ ማግኘቷ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

February 19, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ በ2012 ግማሽ በጀት ዓመት 39 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ብድርና እርዳታ ማግኘቷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ ብድሩ የተገኘው ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት እና ሀገራት መሆኑን አስታውቋል።