የሀገር ውስጥ ዜና

ለኢትዮጵያ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አባላት ስልጠና ተሰጠ

By Tibebu Kebede

February 20, 2020

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ለኢትዮጵያ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አባላት በሀገሪቱ ዲፕሎማሲ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል።

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለኢትዮጵያ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አባላት የሚሰጠውን የአንድ ቀን ስልጠና ዛሬ ጠዋት አስጀምረዋል።