የሀገር ውስጥ ዜና

በተመድ ምክትል ዋና ፀሀፊ የተመራ የመንግሥቱ ድርጅት ልኡክ ኮምቦልቻ ከተማ የጅምላ መቃብር ቦታንና በሽብር ቡድኑ የወደሙ ተቋማትን ጎበኘ

By Feven Bishaw

February 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሀመድ የተመራ የመንግሥቱ ድርጅት ልኡክ በኮምቦልቻ ከተማ የጅምላ መቃብር ቦታንና በሽብር ቡድኑ የወደሙ ተቋማትን ጎበኘ፡፡

ዛሬ ረፋድ ኮምቦልቻ ከተማ የገባው በምክትል ዋና ፀሀፊዋ አሚና መሀመድ የተመድ ልኡካን ቡድን የሽብር ቡድኑ ህወሃት ሰለባ የሆኑ ከተለያዩ የህብረተሰቡ ክፍል የተዉጣጡ አካላትን አግኝተዋል ።