የሀገር ውስጥ ዜና

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ተመድ ለክልሉ ሕዝብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ

By Feven Bishaw

February 09, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ረጂ ድርጅቶች በየጊዜው ጦርነት እየተከፈተበት የሚገኘውን የአፋር ሕዝብ እንዲደግፉ ጥሪ አቀረቡ።

በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምክትል ዋና ጸሐፊ አሚና መሐመድ የተመራ የልዑካን ቡድን ከርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና ከተለያዩ የጎሳ መሪዎች ጋር ወቅታዊ የክልሉን ሁኔታ በተመለከተ ውይይት አድርጓል።