አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተደድር አቶ አሻዲሊ ሀሰን በዛሬው ዕለት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል።
የአማራ ክልል ርዕሰ-መስተዳድሩ ዶ/ር ይልቃል ከፋለ፥ በሁለቱም ክልል ህዝቦች ህገ-መንግሥቱን መሠረት በማድረግ የህዝብ ለህዝብ ግንኘነት በማጠናከር የተጀመሩ የውይይት መድረኮችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በውይይቱ ላይ ተናግረዋል።