ዓለምአቀፋዊ ዜና

የአፍሪካ ሕብረትና የአለም ሠራተኞች ድርጅት በጋራ ለመስራት ተፈራረሙ

By Meseret Awoke

February 11, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ሕብረትና የአለም ሠራተኞች ድርጅት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱን የአለም ሠራተኞች ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ረዳት ዋና ዳይሬክተር ሲንቲያ ሳሙኤል ኦሎንጁን በአፍሪካ ሕብረት የጤና፣ የሰብአዊ መብትና የማህበራዊ እድገት ጉዳዮች ኮሚሽነር ሚናታ ሴሱማ ሰማቴ ጋር መፈራረማቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ከአፍሪካ ሕብረት ጋር የረጅም ጊዜ ትስስራችንን የሚያጠናክር ስምምነት ተፈራርመናል ሲሉ የአለም ሠራተኞች ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ረዳት ዋና ዳይሬክተር ሲንቲያ ሳሙኤል ኦሎንጁን ተናግረዋል፡፡

ስምምነቱ በአፍሪካ አህጉር ሊተገበር የታቀደውን የ2063 አጀንዳ ለማስፈጸም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋልም ብለዋል፡፡

የተመድ የ2030 ቀጣይነት ያለው የእድገት አጀንዳን እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ማኅበራዊ ፍትህን ማስፈን የሚለውን የ2019ኙን የአቢጃን አዋጅ ለማስፈጸም ያግዛል ሲሉም አክለዋል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!