የሀገር ውስጥ ዜና

ወደ መሀል ሀገር ሊገቡ የነበሩና የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው መድሃኒቶች ተያዙ

By Feven Bishaw

February 12, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የማረጋገጫ ፈቃድ የሌላቸውና የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸውን መድሀኒቶች በሲሚንቶ ጭነት ስር ደብቆ ወደ መሀል ሀገር ለማስገባት የሞከረ አሽከርካሪ ትናንት ምሽት በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ።

ሽከርካሪው በኤፍ ኤስ አር የጭነት ተሽከርካሪ መድሀኒቱን በመደበቅ ከሀረር ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እንዳለ በጭሮ ኬላ በተካሄደ ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን የጭሮ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጅን ካሳሁን ባይሳ ተናግረዋል፡፡