የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትጵያዊቷ አጊቱ ጉደታ ገዳይ የ20 ዓመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት

By Feven Bishaw

February 15, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የትሬንቶ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያዊቷ ሥራ ፈጣሪ አጊቱ ጉደታ ገዳይ በሆነው ሱሌማን አዳምስ ላይ የ20 ዓመት ጽኑ እስራት ፈርዶበታል፡፡

ፍርድ ቤቱ ትላንት የካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ባዋለው ችሎት ኢትዮጵያዊቷን ስራ ፈጣሪ አጊቱ ጉደታን ቤቷ ውስጥ በመዶሻ ጥቃት በማድረስ እ.ኤ.አ. ዲሴምበር 29 ቀን 2020 ለህልፈተ ህይወት የዳረገው የ33 ዓመቱ ጋናዊ ሱሌማን አዳምስ ላይ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ውሳኔ አስተላልፏል።