Fana: At a Speed of Life!

ለአንድ ሣምንት ምርቱን አቋርጦ የነበረው የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ዳግም ስራ ጀመረ

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በነዳጅ አቅርቦት ችግር ለአንድ ሣምንት ማምረት አቋርጦ የነበረው የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ዳግም ምርት መጀመሩን የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ገለጸ፡፡

በዓመት 2 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል ስኳርና 20 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል የማምረት አቅም ያለው የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ÷ በነዳጅ እጥረት ምክንያት ለአንድ ሣምንት ማምረት አቁሞ እንደነበር ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን እንዳስታወቀው÷ ነዳጅ ጫኝ መኪና አሽከርካሪዎች ለደኅንነታቸው በመስጋት ወደ አካባቢው ለመሄድ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ከየካቲት 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሣምንት ማምረት አቁሞ ነበር፡፡

ሆኖም ከየካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ አቅርቦት ችግሩ በመስተካከሉ ወደ መደበኛ የማምረት ስራው መመለሱን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በአካባቢው የሸኔ ታጣቂ በመግባት በፋብሪካው ላይ ጉዳት አድርሷል የሚለው መረጃ አሉቧልታ መሆኑን ያመለከተው የስኳር ኮርፖሬሽን÷ ከየካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ መደበኛ የማምረት ስራ ገብቷል።

በኢትዮጵያ ከ1991 ዓ.ም ጀምሮ ስኳር ማምረት የጀመረው የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ እስከ 2003 ዓ.ም ድረስ ብቸኛው የኢታኖል አምራች ሆኖ የቆየም ግዙፍ ፋብሪካ ሲሆን÷ በ1991 ዓ.ም ስኳር ማምረት ሲጀምር የነበረው 6 ሺህ 476 ሄክታር መሬት አሁን ላይ 21 ሺህ ሄክታር መድረሱ ታውቋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.