ዓለምአቀፋዊ ዜና

የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ እና ቱርክ በ13 የኢኮኖሚ ዘርፎች ለመተባበር ተስማሙ

By Feven Bishaw

February 16, 2022

አዲስ አበባ፣የካቲት 9፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ እና ቱርክ በ13 የኢኮኖሚና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ለመስራት መስማማታ ቸዉን አስታወቁ፡፡

የቱርኩ ፕሬዚደንት ረጅብ ጣይብ ኤርዶኻን ከአስር አመታት በኋላ በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፥ ከአቡዲያቢ ልዑል አልጋ ወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዚያድ ጋር ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል፡፡