የሀገር ውስጥ ዜና

አዲስ አበባ ሊገባ የነበረ 2 ሺህ 500 የክላሽንኮቭ ጠመንጃ ጥይት ተያዘ

By Meseret Awoke

February 16, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሱሉልታ ወደ አዲስ አበባ በኤፍ ኤስ አር የጭነት መኪና ተጭኖ ሊገባ የነበረ 2 ሺህ 500 የክላሽ ጥይት በጉለሌ ክፍለ ከተማ የፍተሻ ኬላ ላይ በቁጥጥር ሥር ውሏል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ፥ በፍተሻው ወቅት በጥይት አዘዋዋሪነት የተጠረጠረው ግለሰብና አሽከርካሪው ለጊዜው ቢሰወሩም ፖሊስ ክትትሉን ቀጥሏል ብለዋል።

ተሽከርካሪው እና ጥይቶቹ በቁጥጥር ሥር ውለው በኤግዚቢትነት የተያዙ ሲሆን፥ የፖሊስ ምርመራ እየተካሄደ እንደሆነ መግለጻቸውን ከአዲስ አበባ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል:: ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!