Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ፍሪያማ ውይይት አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ገለጹ፡፡

ውይይቱን አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ “ከወንድሜ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት እና አኅጉራዊ ጉዳዮች ላይ ስለ ነበረን ፍሬያማ ውይይት ምስጋናዬ ይድረስ” ብለዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የዳበረ ግንኙነት ለቀጣይ ትብብር ጠንካራ መሰረትን የጣለ ነው ሲሉም በመልዕክታቸው አስፍረዋል፡፡

 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቤልጂየም ብራሰልስ እየተካሄደ በሚገኘው 6ኛው የአውሮፓ ኅብረት እና አፍሪካ ኅብረት የጋራ ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.