የሀገር ውስጥ ዜና

የአዳማ ሪፌራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የህክምና ዶክተሮችን አስመረቀ

By Tibebu Kebede

February 22, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዳማ ሪፌራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌና ከፍተኛ የቀዶ ህክምና ስፔሻልስቶችን ጨምሮ በተለያዩ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን 140 ዶክተሮችን ዛሬ አስመረቀ።

ከተመራቂዎቹ መካከል ደቡብ ሱዳን የህክምና ስፔሻልስቶች ይገኙበታል።