የሀገር ውስጥ ዜና

የሲቪክስ የፈተና ውጤት ለዩኒቨርስቲ መግቢያ መወዳደሪያነት እንዳያገለግል ተወሰነ

By Feven Bishaw

February 23, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲቪክስ የፈተና ውጤት ለዩኒቨርስቲ መግቢያ መወዳደሪያነት እንዳያገለግል መወሰኑን ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

ኤጀንሲው ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው ማብራሪያ፥ የ2013 ዓ.ም 12ኛ ክፍል የኢትዮጵያ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና እርማቱ ደህንነታቸው አስተማማኝ በሆኑና ከንክኪ ነጻ በሆኑ የማረሚያ ማሽኖች አስፈላጊው የደህንነት ጥበቃ በፌደራል ፖሊስና በሴኩሪቲ ካሜራዎች ታግዞ በጥንቃቄ መከናወኑን ገልጿል፡፡