አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ተቋማት የአሰራር ግልጽነትና ገለልተኝነት በተግባር እየተረጋገጠ መምጣቱን በጠቅላይ ሚኒስትር ዕህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ዶ/ር ቢቂላ ሁሪሳ ገለጹ።
ዶክተር ቢቂላ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ እስካሁን ነጻና ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መፍጠር፣ ጠንካራ ምርጫ ቦርድ ማደራጀትና የፍትህ ስርዓቱን የማሻሻል ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።