የሀገር ውስጥ ዜና

በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 14 ክላሽ ጠብመንጃ ተያዘ

By Tibebu Kebede

February 23, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢሉ አባቦር ዞን ቡሬ ወረዳ በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 14 ክላሽኮቭ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገለፀ።

የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ታረቀኝ አሰፋ እንደገለፁት፥ የጦር መሳሪያው የተያዘው በሚኒባስ ተሽከርካሪ ከጋምቤላ ወደ አዲስ አበባ በመጓጓዝ ላይ እንዳለ ነው።